Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 223 ስንጨነቅ ስናዝንም የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ስንጨነቅ ስናዝንም
ተስፋ ቈርጠን ስንባዝን፥
አትተወን አምላካችን ደግፈን
በጅህ ምራን።
ስንጨነቅ ስንፈራ፥ ጌታ ሁን
ከኛ ጋር፤
ስንጨነቅ ስንፈራ፥ ጌታ ሁን
ከኛ ጋር።
፪፡ ሰው ሲጠላን ስንሰደድ
መከራችን ሲበዛ፥
ከኛ ጋር ሁን አምላካችን የሱስ
ሆይ የኛ ቤዛ።
ስንጨነቅ፡፡.።
፫፡ መንፈስ ቅዱስህ ያበርታን
መከራን እንድንችል፥
ስንጨነቅ ስንፈተን
ሃሌ ሉያ እንድንል።
ስንጨነቅ፡፡.።
፬፡ ዘመናችን ቶሎ ያልፋል
ምንም ብንጨነቅም፥
የሱስን ግን ብንተወው
የለንም አንዳች ጥቅም።
ስንጨነቅ፡፡፡.።
፭፡ ወንድሞቼ እኀቶቼ
በጣሙን እንበርታ፥
ኢየሱስን እንመንው
ለሰይጣን አንረታ።
ስንጨነቅ፡፡.።
፮፡ በመከራ ሊያበረታን
ታላቅ ተስፋ የሰጠን፥
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ
አምላካችን ይመስገን
ስንጨነቅ፡፡.።