Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 202 ምን እመልሳለሁ ለአምላኬ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ምን እመልሳለሁ ለአምላኬ
ላደረገልኝ በጎነት ሁሉ
በርሱ ድኗል መላ ሕይወቴ
ነግሮኛል በቅዱስ ቃሉ።
የሚያስጨንቀኝ ነገር ምንድን ነው?
በ – ቅዱስ ስሙ አምኜአለሁ
እርሱ ራሱ ከእኔ ጋር ነው
ለምንስ እጨነቃለሁ።
፪፡ በሃይማኖት ስሙን የሚጠራ
ከመከራ ፈጽሞ ይድናል
ይሆንለታል ታላቅ ደስታ
በረከትንም ያገኛል።
ሞ – ትን ሳይፈራ ለዘላለም
ሁ – ል ጊዜ ይኖራል በእምነት።
ክፉ ጭንቀት አያገኘውም
ይጠበቃል ባምላክ ምሕረት።
፫፡ በቃሉ ሲጠራኝ አልዘገይም
አቀርባለሁ ወደ እርሱ አሁን።
ያለ እርሱ ሌላ የለኝም
የሚሆነኝ ታላቅ መድኅን።
አ – ልመካም በሌላ ነገር
ቅዱስ መንፈሱ ይረዳኛል።
እንዳይገባብኝም ጥርጥር
በፍቅሩ ይታደገኛል።