Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 195 አምላክ በምሕረቱ ብዛት የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አምላክ በምሕረቱ ብዛት
ለሕይወት መረጠነ
በየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ደም
ከኃጢአት አጠበነ።
ትምክህታችንን አስቀረ
ዕዳችንንም ከፈለ
በጸጋው ይቅር አለን።
፪፡ የአምላክ ትእዛዝ ቅዱስ ነው
መታዘዝ ግን አቃተን
አዳም ከበለስ ፍሬ በልቶ
ሁላችንን አሳተን።
ከርሱ የምንወለድም
ያምላክን ሕግ ፈቃዱንም
መፈጸሙን አልቻልንም።
፫፡ ሕግ ሁሉ ግን እስኪፈጸም
ከፍርድ አናመልጥም
የወልድን ጽድቅ ካልለበስን
ሕይወትን እናገኝም።
ጌታ ሆይ እናመስግንህ
ከዘለዓለም ኩነኔ
በልጅህ ስላዳንከን።
፬፡ ያለምን ሁሉ ኃጢአት
ሲሸከም የመጣልን
ያምላክ ልጅ በመስቀል ሲሞት
ኦሪትን ፈጸመልን።
መድኃኒታችን የሠራውን
በእምነት ብንቀበለው
ሕጉ አይፈርድብንም።
፭፡ የአቅማችንን ድካም
አውቀን በአዳኛችን
በፈጸመልንም ሕማም
በደሙም ኃይል ስናምን
ጽድቁ ይቆጠርልናል።
በአምላክ ፊት ያጸድቀናል።
ልጆቹም ያደርገናል።
፮፡ የአምላክ ልጆች ከሆንን
መንፈሱ ይመራናል።
የመንፈስን ፍሬ ለማፍራት
በእውነት ይረዳናል።
ምእመናን ሁላችንም
በተስፋና በእምነት ጸንተን
ሰማይ እንገባለን።
፯፡ አምላክ እኛን ኃጢአንትኞች
በምህረቱ አናነን
ጸጋውንም ሊያካፍለን
ቅዱስ ፈቃዱ ሆነ።
ምስኪኖች ጐስቋሎች ነን
የሱስ ግን ስለወደደን
ጽድቅና ሕይወት ሆነን።