Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 190 ለዓለም ሕይወት ልትዋጅ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ለዓለም ሕይወት ልትዋጅ፥
የእኛን ሥጋ ለበስህ።
በሰማይ ቤት ልታዘጋጅ፥
ኦ የሱስ ሞትን ቀመስህ።
ሲኦል ተከፍቶብን ሳለ፥
የአምላክ ምሕረት ተሰጠን፤
ፍጹም አርነት ወጣን።
፪፡ አንተም ስታይ የኛን ጥፋት፥
በፍቅርህ ራራህልን።
ልታድነንም ከሥቃይ፥
ወደዓለም መጣህልን።
በአንተ ሞትና ሕማም፥
የእግዚአብሔር ሰላም
ኦ የሱስ ተገኘልን።
፫፡ በትሩፋትህ አምነን
ወዳንተ ስለ መጣን፥
ሙሉ ይቅርታ አገኘን፤
በሕግህ ሳትቀጣን።
እኛ ይህን ተቀብለን፥
በቅዱስ ቃልህ ታምነን
ከሞት እንድናለን።
፬፡ ቸር ወንድማችን አንተ ነህ፤
እንዴት አፍቅረኸናል።
ዘላለም ከኛ ጋር ነህ፤
ሁሉንም ሰጥተኸናል።
የዓለም ስድብና ጥል
ከቶ ሊጎዳን እንዳይችል፥
ያምላክ ልጅ አምባችን ነው።
፭፡ ግሩም ጸጋህን የሰጠኸን
ጌታችን ሆይ ተመስገን።
በደምህ ስለ አዳንኸን፥
ልጆችህ አደረግኸን።
አምላክንም እናመስግን፥
እርሱ በየሱስ ክርስቶስ ስም፥
ቸር አባታችን ሆነ።