Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 161 ሰው በጭንቅ በደስታም ቢኖር የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ሰው በጭንቅ በደስታም ቢኖር፥
የሞቱ ቀን ይደርሳል።
በዓለሙ የትም ቢዞር፥
ከመሞት አያመልጥም፥
ሊመርጥም አይችልም።
ጊዜው ከደረሰ፥
መመለስ አይሆንለትም፤
ምድራዊ ተስፋው ፈረሰ።
፪፡ ግን በየሱስ የሚያምን፥
ወደ ሰማይ ይሄዳል።
በመሬት ውስጥ ቢቀበርም፥
በሰማይ ዘውድ ያገኛል።
ብፅእናን መርጦአል፤
አይወሰድበትም።
በየሱስ ሞት ጸድቆአል፤
የሰማይ ርስቱን ይወርሳል።