Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 158 አምላክ ሆይ በቸርነትህ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አምላክ ሆይ በቸርነትህ
ሙሽሮችን ባርካቸው።
አጽና ኪዳናቸውንም
ቀድስ አንድነታቸውን።
በደስታ ሆነ በኅዘን
ስጣቸው ፍቅር ሰላም
ዘወትር ሁናቸው ተገን።
፪፡ ብፅዕናን አድላቸው
በፍርሃትህ አጽናቸው።
ፈተና ሲደርስባቸው
አንተ ረድኤት ሁናቸው።
ቢከብሩ ቢዋረዱ
ቢያገኙ ቢያጡ
በትዕግሥት ይኑሩ።
፫፡ በዓለም በሚቆዩበት
ባንተ ምክር ምራቸው።
እንዲረዳዱ በትዕግሥት
በጸጋህ ደግፋቸው።
ቸርነትህ አይለያቸው
ምሕረትህንም ስጣቸው
እስኪፈጸም እድሜአቸው።
፬፡ ባንድነት በሚኖሩበት
ሁናቸው ኃይልና ብርታት።
ለምስጋናህ እንዲኖሩ
በመንፈስህ ይመሩ።
ረጅምም እድሜ ስጣቸው
እርጅና ሲጫናቸው
ልጆች ይደግፉአቸው።
፭፡ የሞታቸው ጊዜ ሲደርስ፥
ሁለቱን ሲለያቸው፥
አንዱን ሞት ነጥሎ ሲወስደው
ቤቱን ኃዘን ሲሞላው
ኀዘንተኛውን አጽናናው።
ሞት ፍጹም በሌለበት
በሰማይ አኑራቸው።