Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 134 አምላክ ሆይ በጸጋህ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አምላክ ሆይ በጸጋህ ዓይኔን ክፈትልኝ
ያፍህን ሕግ አስተምረኝ።
የእጅህን ሥራና ታምራት አይ ዘንድ
ሕግህን ዘወትር አስተምረኝ።
የ – አፍህ ሕግ ይሻለኛል
የ- አፍህ ሕግ ይሻለኛል
ከሚጠፋ አእላፋት ወርቅና ብር
የ – አፍህ ሕግ ይሻለኛል።
፪፡ ትእዛዝህ እጅግ በጣም ደስ ያሰኛል
ያፍህን ሕግ አስተምረኝ።
የዋሐንን ደግሞ ጠቢባን ያደርጋል
ሕግህን ዘወትር አስተምረኝ።
የ . አፍህ ሕግ . . .።
፫፡ ጽድቅህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ናት
ያፍህን ሕግ አስተምረኝ።
በቅዱስ መንፈስህ አስተዋይ አድርገኝ
ሕግህን ዘወት አስተምረኝ።
የ – አፍህ ሕግ . . .።