Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 110 በቶሎ ይመለሳል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በቶሎ ይመለሳል
ሰማያዊ ጌታ፤
ሙሽራይቱን ከውርደት
ያነሣል ለክብረት።
የጽድቅ ልብስ ያለብሳታል፤
አክሊል ይሰጣታል።
የሞቀው የጥንት ፍቅር
ይመለስላታል።
፪፡ እንቅልፍ የከበደባት
ሙሽራይቱ ትንቃ፤
ከፍርድ ነጻ መሆንዋን
ድንቅ ተስፋውን ትስማ።
ለጠፉት ልጆች ሁሉ
አምላክ መራራቱን፤
በብርሃን መምራቱን
አማኝ ሁሉ ያውራ።
፫፡ እናንት አሕዛብ ተንሡ፤
የሱስን እመኑ።
ሕይወት እንድታገኙ፥
በርሱ ብቻ ጽኑ።
በእምነት በርትታችሁ
ፍቅራችሁን ግለጡ፤
ሕዝብ ወንጌልን ሲቀበል
መዳኑን እወቁ።
፬፡ የሱስ መንኃኒታችን
በቅዱሳን መላእክት
ታጅቦ ይመለሳል።
በዚያ በፍርድ ዕለት
ሕዝቦች ሁሉ በፊቱ
ለፍርድ ይቀርባሉ።
ጻድቃን፥ ግሩም ብጽዕና
በላይ ያገኛሉ።