Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 109 በምን መሠረት ሠርተሃል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በምን መሠረት ሠርተሃል?
ከፍርድ እንድትድን።
በየሱስ ብቻ ተስፋህን
ማድረግ ይበቃሃል።
ቢሉኝ ምላሼ እንዲህ ነው፥
መሠረቴማ ጽኑ ነው፤
እርሱም መድኃኒታችን ነው፤
ደሙም ሕማማቱም።
፪፡ አንድ ዓለት ይህ መሠረት ነው፤
ዘላለም የማይወድቅ።
የሕይወት ዘመኔም ሲያልቅ፥
ዕረፍቴ በርሱ ነው።
ከምድር ስሰናበትም፥
ልዘምር ስለ የሱስ ደም።
አሁንና ዘላለምም
ተስፋዬ እርሱ ነው።