መዝሙር 500 የጌታ አገልጋይ እንድትሆን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የጌታ አገልጋይ እንድትሆን
ቃሉን በደስታ እንድትሰብክ።
የራቁ የጠፉትን ለመጥራት፥
ሁሉንም ወደ እርሱ ለማምጣት።
ትጠራለህ ቶሎ ብለህ ሂድ
ትጠራለህ ቶሎ ብለህ ሂድ።
የመዳንን ጊዜ ንገራቸው
የጌታን ተስፋ በማስተማር።
፪፡ የጌታህን ተስፋ አብሥራቸው
በክፋት ለሚገኙ ሰዎች።
ለታሰሩ በኃጢአት ባርነት፥
ነጻ ለማውጣት አድርግ ጥረት።
ትጠራለህ . . .።
፫፡ በኢየሱስ ስም መዝሙር አዘጋጅ
ለድካሙና ሥቃይ ሞቱም።
ሁሉን በፍቅሩ የተሸከመ
ነፃ እንዲያወጣን ከኃጢአት።
ትጠራለህ . . .።