መዝሙር 476 አንድ ነን በመንፈሱ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አንድ ነን በመንፈሱ አንድ ነን በጌታ(2)
ይህንን ለማስታወቅ በፍቅር አንበርታ።
አንድነታችንን አሕዛብ ያያሉ ያያሉ
በፍቅር አንድነታችንን ያውቃሉ።
፪፡ ባንድ መንፈስ ተጠምቀናል ባንድነት እንሄዳለን(2)
እርስ በርስ በመስማማት በፍቅር እንኖራለን።
አንድነታችንን አሕዛብ ያያሉ ያያሉ
በፍቅር አንድነታችንን ያውቃሉ።
፫፡ ባንድነት ተባብረናል ባንድነት እንሠራለን(2)
የአምላካችንን ህልውና እናውጃለን።
አንድነታችንን አሕዛብ ያያሉ ያያሉ
በፍቅር አንድነታችንን ያውቃሉ።
፬፡ ምስጋና ለእግዚአብሔር ስለ ስጦታው ሁሉ
ምስጋና ለኢየሱስ ክርስቶስ ለልጁ።
ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ ስለ ሰጠን ኅብረት
አንድነታችንን አሕዛብ ያያሉ ያያሉ
በፍቅር አንድነታችንን ያውቃሉ።