መዝሙር 450 ቅዱስ አምላክ ሆይ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ቅዱስ አምላክ ሆይ፥ ባንተ ፊት
ሕዝብህ የሚቀርብበት፥
ያ ብሩክ ቀንህ ይምጣለት።
አውርድለት በረከት፥
በዚያን ጊዜ ስብሐት፥
ይቀርባል ከአእላፋት።
፪፡ ምሥራቅ ምዕራብ ደቡብ ሰሜን
ይድረስ የወንጌል ትምህርት።
በምድር ግርማህ ይገለጥ፥
ላንተ ይሁን ታላቅነት።
አብዛ ምእመናንህን፥
ስጣቸው ሰላም ደስታን።
፫፡ ትሰማለህ ስንለምንህ
ቢዘገይብን እንኳ፤
አሕዛብን ለማሳመን፥
ለፍቅርህ የለውም ወሰን።
ጸጋህን ለምታሳይ፥
ስብሐት ላንተ በሰማይ።