መዝሙር 432 ከከንቱ ዓለም የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከከንቱ ዓለም
ስጓዝ ወደ ሰማይ።
ቶሎ ደከምኩኝ፥
የሱስ ግን ደገፈኝ።
በእጁም ያዘኝ፥
በፍቅሩ ረዳኝ፥
በፍቅሩ ረዳኝ።
፪፡ ስራመድ ሳለሁ
ወደ ላይኛው ቤት።
በላዬ ያለውን፥
የኃጢአት ሸክሜን፥
አይቶ ችግሬን፥
አወረደልኝ፥
አወረደልኝ።
፫፡ ከባድ ሸክሜን
አነሣልኝ በጁ፥
ዕረፍትም ሰጠኝ፥
አቀፈኝ በክንዱ።
እየመራኝም፥
ቤቱ አስገባኝ፥
ቤቱ አስገባኝ።
፬፡ የዓለም መድኅን
ስለኛ የሞትህ፥
ሕይወት የሆንህ።
በኃጢአት ለሞቱ፥
ለእኔ ደግሞ፥
ሕይወትን ሰጠኝ፥
ሕይወትን ሰጠኝ።