መዝሙር 331 የሱስ ሆይ ጸሎቴን ስማኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ሆይ ጸሎቴን ስማኝ
ዞትር አትለየኝ።
በምሄድበትም መንገድ
ፍቅህንም አውርድ።(2)
፪፡ መንፈስ ቅዱስህን ላከው
ልቤን እንዲያሞቀው።
የሰማዩን ቤቴን እንዳይ
ከዳኑት ባንድ ላይ።(2)
፫፡ አምላኬ ሆይ እኔን እርዳኝ
በጣም ደካማ ነኝ።
ኃጢአቴ የከበደኝ
ጐስቋላ ምስኪን ነኝ።(2)
፬፡ ጊዜያቱ ሲመሽብኝ
ጌታ ሆይ ጠብቀኝ
ከእኔ ዘንድ አትራቀኝ
ለብርሃንህ አብቃኝ።(2)
፭፡ ያንተ ናቸው ክብር ኃይልም
ዛሬና ዘወትር።
ምስጋና ለስምህ ይሁን
ለዘላለም አሜን።(2)