መዝሙር 314 በዚህ በእንግድነቴ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በዚህ በእንግድነቴ
ልቤ ለምን ይፈራል?
ያ እሙኑ መድኃኒቴ
አካሄዴን ያቀናል።
የሞተው ስለ በጎቹ
በቃሉና በመንፈሱ
ከእኔ ጋር ይኖራል።
፪፡ እከተላለሁ ፈለጉን
ድምፁንም እሰማለሁ።
ቸር እረኛችን ትጉ ነው
በጎቼን ሁሉ ያውቃል።
የጠፉትን ይፈልጋል
የደከመውን ይሸከማል
የወደቀውን ያነሣል።
፫፡ ከሕይወት ኅብስት ያበላል
ከጸጋ ምንጭ ያጠጣል።
በመንፈስ ኃይል ያበረታል
ሰላሙንም ይሰጣል።
በጨለማ እንኳ ብሄድ
እርሱን ተከትዬ ስሄድ
አንድ ቅዱስ ድፍረት አለኝ።
፬፡ በጌን በኃይል ከመንጋዬ
የሚነጥቅብኝ የለም።
ያልከው ቸር እረኛዬ ሆይ
ና ጠብቀኝ ከዓለም።
ይህ ዓለም በከንቱነቱ
በእጅህ ከሚመሩቱ
አይለየኝ ለዘላለም።
፭፡ ይህ ሐይወት እንደ ሕልም ያልፋል
በረን እንሄዳለን።
ቀናችን ይመሽብናል።
ከዚህ እንጓዛለን።
ሲያልፍም እንግድነቱ
እንዳልኸን ባለህበቱ
እኛም እንሆናለን።