መዝሙር 298 ስትጨነቅ ሳለህ ጥራ የሱስን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ስትጨነቅ ሳለህ ጥራ የሱስን
እርሱ የአንተ ረዳት ነው።
ድካምህንም ግለጥለት አሁን
ችግርህንም ንገረው።
በታላቅ ኃይሉ ሊያበረታህ ነው
ግን በራስህ ኃይል ፈጽመህ ሙተሃል።
ስለዚህ ቸኩል ወደ የሱስም ሽሽ
የጸጋ ኃይሉን ልበሰው።
፪፡ አምላካችን ጭንቅህን ሁሉ ያያል
ጩኸትህንም ይሰማል።
የሚያድስ ኃይልም ይሰድልሃል
በእምነት ብቻ ተቀበል።
አንተን ይወዳል አንተን ይረዳልም።
ነፍስህ እንድትሞት ከቶ አልወደደም
ስለዚህ የሱስን ሊሠዋ ላከው
በሞቱ አንተን አዳነ።
፫፡ ችግርህን እስኪያስወግድ ቢዘገይ
በጭንቀት ስትጐሰቍል።
ወደ ላይ አሻቅበህ የሱስን እይ
ችግርህንም ያርቃል።
ተስፋህ አድርገው ለመላው ዘመንህ
እርሱ ኃይልህ ነው ከሞትም ያዳነህ።
ብርሃኑ ይሠራል በልብህ ገብቶ
ዕውርነትህን ያበራል።