መዝሙር 222 ያምላካችን ታናሽ ጭፍራ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ያምላካችን ታናሽ ጭፍራ
ቤቱ ነው በጽኑ ስፍራ
የለም የሚያስፈራራው
አምላክ ይሆነዋል ጋሻ።
፪፡ ልጆቹ ባምላክ ተራራ
ይኖራሉ ከርሱ ጋራ።
እርሱም ልጆቹን ይጠራል
ሰርክ ሲጠብቅም ይኖራል።
፫፡ ደስታ ሆነ ወይም ጭንቀት
ልጁን ከርሱ እጅ አይነጥቅም
ያ ወዳጅ በጽኑ እጁ
ጋሻ መክቶአል ለልጁ።
፬፡ የራስ ጠጉራችን ሁሉ
ባምላክ ዓይን ይቆጠራሉ።
አምላክም ይመግበናል
በርሱም ፍቅር ደስ ይለናል።
፭፡ ቢሰጠንም ቢነሣንም
አባትነቱን አይረሳም።
ሐሳቡም ለጥቅማችን
ነው በመላ ዘመናችን።
፮፡ ደስ ይበልህ ታናሽ መንጋ
አምላክህን አትዘንጋ።
ጠላቶችም ቢነሡብህ
በእርሱ ኃይል ይጠፋሉ።