መዝሙር 194 የጌታችን የየሱስ ሞት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የጌታችን የየሱስ ሞት
ለነፍሳችን ሆነ ሕይወት።
ጸጋና እውነት ሰላምም
አግኝተናል በርሱ ሕማም።
፪፡ ደሙን ስለ አፈሰሰ
ዕዳችን ተደመሰሰ።
በፍቅሩ ስለ ወደደን
ከአምላክ ጋር አስታረቀን።
፫፡ ጌታችንን እንመነው
ጸጋውን እንቀበለው።
መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል
ቁርባኑንም ሠርቶልናል።
፬፡ ቅዱስ ሥጋውን ሰጥቶናል፤
ቅዱስ ደሙም ቀርቦልናል።
እንዲሆን ለሕይወታችን
እንውሰደው በልባችን።
፭፡ ይህ ሰማያዊ መና ነው
ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።
በእምነት ስንቀበለው
ሕያዋን ነን ለዘለዓለም።