መዝሙር 190 መተላለፉ በደሉ የቀረችለት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መተላለፉ በደሉ የቀረችለት
ኃጢአቱም የተከደነችለት፥
በአምላኩ ምሕረት ብቻ የሚተማመን፥
በንሰሐ የሚቀርብ ሰው ብቻ ቡሩክ ነው።
፪፡ ኃጢአታችንን በፊቱ ብንናዘዝ
በጸጋው ይቅርታ ይከድነዋል፥
እንደ ዓይኑ ብሌንም ይጠብቀናል፥
በፍቅሩ ብርታት ልጆቹን ይታደገናል።
፫፡ አማላጃችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው
በመስቀል ላይ የሞተልን እርሱ ነው።
በትንሣኤው ሞትን ሽሮ ድል የነሣ፥
የኢየሱስ ደም ብቻ ነው የእኛ ተስፋ።
፬፡ በግርማው ፊት እንንበርከክ በንስሐ
መነገድ እውነት ሕይወት የሱሰ ነውና።
ከለላ አምባችን መጠጊያችን እርሱ ነው፥
የዘለዓለም ሕይወት ተስፋችን እርሱ ነው።