መዝሙር 126 አምላኬ ሆይ በኃጢአቴ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላኬ ሆይ
በኃጢአቴ፥
ከባድ ኅዘን ተሰማኝ፥
በዚች ዓለም
አንድ ሰው የለም፥
በጭንቀት የሚረዳኝ።
፪፡ ሩቅም ብሄድ፥
ረጅም መንገድ፥
እስከ ዓለም ዳርቻ።
ከየት ላግኝ
ደስታን ሰጥቶ፥
ከኅዘን የሚፈታኝ
፫፡ ቸር አምላኬ
ወደ አንተ፥
እመጣለሁኝ አሁን።
አባት ሆነህ
ተቀበለኝ፥
ዘወትር ተገን ሁነኝ።
፬፡ ቸሩ የሱስ
ደካማ ነኝ፥
ለውጥ ክፉ ጠባዬን።
ትዕግሥት ስጠኝ
አጠንክረኝ፥
በደስታና በኅዘን።
፭፡ ባንተ ፈቃድ
በቅን መንገድ፥
እንድሄድ አንተ ምራኝ።
በዚች ዓለም
ብርቱ ሸክም፥
ልታገሥ ኃይልን ስጠኝ።
፮፡ አብና ወልድ
በባሕርይ አንድ
ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ
ስማኝ አሁን
አዎን አሜን
ጸሎቴን ትሰማለህ።