Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 85 በአምላክ ተመርተን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በአምላክ ተመርተን በቃሉ ብርሃን
በልጁም ሲጸና የምሕረትህ ኪዳን
ያላየነው ዘመን ሲቀርብ እንፍራ።
ያ ቸር እረኛችን
ሲኖር በቅርባችን
ሲሄድ በፊታችን
ከምን እንፍራ?
፪፡ ከጨለማ ዓለም ከምድር ሥቃይ
አንድ ጭፍራ ተነሣ
ሊጓዝ ወደላይ
የጭፍራው ገናንነት
ተሰውሮአል።
ግን አምላክ ሲቀድም
ሲከተል ሲከብም
ሲደግፍ ሲሸክም
ይጋርደዋል።
፫፡ ከንቱነቱን ዓለም ሲፈልግ ሲሻው
በርኩሰትም ብቻ ሲሆን ደሰታቸው
ያን ጭፍራ ልከተል
ሲሄድ ወደ ላይ
ያልታሰበውን ክብር
ያልታየውን ምስጢር
የተስፋውን ነገር
ላገኝ በሰማይ።
፬፡ የደመና ዐምድ የእሳት ብርሃንም
ውኃ የሚሰጠው ሕያው ዓለትም።
ዘወትር ሊመሩን ይከተሉናል
ያንን ቅዱስ ዓለት
ብናምነው በእውነት
ለሞቱቱ ሕይወት
ሊሰጥ ይችላል።
፭፡ ያ ዓለትም ክርስቶስ አዳኛችን ነው
ያነጻንም ደም የወጣበት ውኃው።
የኃጢአታችን ሥርየት አለነ
በአንዱ በየሱስ
ያ ጻድቅ ያ ቅዱስ
ለምስኪን ስርኵስ
መድኃኒት ሆነ።
፮፡ በሰይጣን ስጨነቅ ተስፋ ስቆርጥም
መድኃኒቴ ሆነ የልቤ ሰላም
በመስቀሉ ሞተ ለሁሉ ኃጥአን።
ለሁሉም ከሞተ
ሁላችንም ሞትን
ለሁሉም ከሞተ
ተገኘ መዳን።
፯፡ በአምላኬ ፊት በደለኛ ስሆን
በየሱስ ሳምን ማን ይከሰኝ ይሆን?
በየሱስ በልጁ የጸደቅሁ ነኝ።
በእርሱም ሲያየኝ
አንድ ርኵሰትም የለኝ።
ያምላክ ሥምረት አለኝ
በየሱስ ስገኝ።
፰፡ ቃሉም የብፅዕና መያዥዬ ነው
የየሱስ ሥቃል መጽናናቴ ነው
በሞቱ በትንሣኤው አድኖኛል።
መድኃኒቴ ሳለ
ረድኤቴ ዘወትር አለ።
መድኃኒቴ ሳለ
በተስፋ ልኑር።
፱፡ ኦ የሱስ ያልተውኸን እስከ አሁን
መታመንህ ብቻ ተስፋችን ይሁን
ተሸከመን ጋርደን
ከእኛም ዘንድ ሁን።
አሜን ለዘላለም
ምስጋና ስብሐት
ለአምላክ ለበጉም
ሳይጨረስ ይሁን።