Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 328 አንዲት ከተማ አየሁ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አንዲት ከተማ አየሁ
ማንም ያላያትን፥
ውበትዋ ዕፁብ ድንቅ ነው።
ሌሊት የለባትም
ብርሃንዋ የሱስ ነው፤
ለዘላለም የሚያበራላት።
እመኛለሁ፤ እመኛለሁ፥
በዚያች ከተማ ውስጥ ለመኖር።
እመኛለሁ፥ እመኛለሁ፥
ከጌታ ከየሱስ ጋራ ለመሆን።
፪፡ ከከተማው መሐል
ከበጉ ዙፋን ሥር
የሚወጣ የሕይወት ምንጭ አለ።
ለሚጠጡት ሁሉ
ሕይወትን ይሰጣል፤
ዳግመኛ መጠማት አይኖርም።
እመኛለሁ . . .።
፫፡ ከዚህ ዓለም ስለይ፥
ዘመኔን ጨርሼ
ችግርና ሥቃይ ቀርቶ፥
በዚያች ከተማ ውስጥ
ለሚነግሠው ንጉሥ
ለዘላለም እዘምራለሁ።
እመኛለሁ . . .።