Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 316 የሱስ ነው የእኔ ተስፋ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ነው የእኔ ተስፋ፤
ሞትን ድል ነስቶ ተነሣ።
እውነትን ተረዳሁ
ኀዘንም፥ ትካዜም ጠፋ።
የሞት ሌሊት ይነጋል፥
ጨለማውም ይጠፋል።
፪፡ ሕያው ነው መድኃኒቴ፥
እኔ ሕይወትን እንድወርስ
ይተባበራል ከኔ።
ሰበብ የለኝም ለማልቀስ
ቸር አበት ከፍቶ ቤቱን
ያስገባልም ልጆቹን።
፫፡ ከእርሱ ጋር ልተባበር፤
በእምነት ጸንቼ ልኑር።
በሕይወት ቢሆን በሞት
ጽኑ ብፁዕ ተስፋ አለኝ።
ከጌታ የሚለየኝ
አንድ እንኳ ባለም አይገኝ።
፬፡ ከንቱ ሥጋ ነኝና
ወደ መሬትም ልመለስ።
ያስነሣኛል ግን ጌታ
ክቡር መንግሥቱን እንድወርስ
ከመድኃኒቴ ጋራ
ልነግሥ ነው በብፅዕና።
፭፡ በሽታ ያማቀቀው
ድኖ በሰማይ ይኖራል።
በውርደት የተዘራው
ቆይቶ በክብር ይነሣል።
የምድሩ ሕምሕምታ
ይለወጣል በልልታ።
፮፡ በደስታ ዘምሩ
የሱስ ልጆቹን ይጠራል።
ሰዎች ሞትን አትፍሩ፤
ብንሞትም ያስነሣናል።
ሙታን ድምጹን ሲሰሙ
ከመቃብር ሊወጡ።
፯፡ ከከንቱ ዓለም ራቁ፤
በእርሷም አትታለሉ።
እንድትሞቱ በተስፋ፥
በሰማይ ያለውን እሹ።
ብትመኙ ብፅዕናን፥
አሁን ሁኑ ቅዱሳን።