Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 108 በጌታ የሱስ ለሚያምኑት ሁሉ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በጌታ ኢየሱስ ለሚያምኑት ሁሉ
ዕለተ ፍርድ የእልልታ ቀን ነው።
በዕለተ ፍርድም ሰላም ያገኛሉ
መከራ ሁከትም የማይነካው።
ትግል ድካም ያልፋል ሁሉም
ክብር ይተካል በውርደት ፈንታ።
፪፡ አልተዘጋጀሁም ሲል የሚፈራ
እንዳይደርስበት በድንገት ያ ቀን።
እርሱ በፍጥነት ወደ የሱስ ይምጣ፤
በትሩፋቱ በቁስሉም ይመን።
በክርስቶስ ደም በሥቃዩም
አምኖ ከሞተ ያገኛል ሰላም።
፫፡ ሞትና ፍርድ እስካሁን ቢያስፈራህ
የየሱስ ክርስቶስን ሞት አስበው።
ከኃጢአትና ከሞት ሊያድንህ፥
እርሱ ቅጣትህን ተቀበለው።
እንዳዳነን የሚያምን
በዕለተ ፍርድ ያገኛል ምሕረት።
፬፡ ኦ ጌታ ሆይ፥ የሱስ ግለጥ ለልባችን
ምን እንደሆነ ያንተ ትሩፋት
አንተ ከሞትህ ስለ ኃጢአታችን
ዳንን ሁላችን ከፍርድና ሞት።
እምነት ስጠን በፍርድም ቀን
ከበጎችህ ጋር በቀኝ አድርገን።