Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 204 እንደ የሱስ መድኃኒታችን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ እንደ የሱስ መንኃኒታችን፥
ወዳጅ የለም፤
ጌታ ሆኖ አብሮኝ ይኖራል፤
ግሩም ፍቅር።
በዓለም ውስጥ ያለው ሁሉ ሲያልፍ፥
ጌታ ግን ለዘላለም ይኖራል።
ልቤን አንጽቶ ሰላም ሰጥቶኛል፤
ግሩም ፍቅር።
፪፡ ኃጢአቴን ሁሉ ሊሰርይልኝ
የሱስ ሞተ፤
ለዘለዓለም ሕይወት ሊያወርሰኝ
እርሱ ሞተ።
የጠፋች ነፍሴን እርሱ ፈለጋት፥
ጸጋ ሊሰጣት ወደርሱ ጠራት።
ከዚያም በክብሩ ይጠብቃታል፤
ግሩም ፍቅር።
፫፡ እከተላለሁ የሚያፈቅረኝን
መድኃኒቴን፤
ሕይወቴን ሙሉ እሰጠዋለሁ
ለየሱሴ።
በመተናኮል ሊያታልለኝ
ያ ክፉ ጠላቴ ቢመጣብኝ፥
ግን ጌታ የሱስ ይጠብቀኛል።
ድል የኔ ነው።