Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 62 በራቀው ኮረብታ የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 62 በራቀው ኮረብታ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ በራቀው ኮረብታ
አስጨናቂ መስቀል
ቆሞአል ለብሶ የጭንቅ ኃፍረት።
እኔ እወደዋለሁ
አስጨናቂውን መስቀል
ያለም መሥዋዕት ስለሞተበት።
ልምረጠው አስጨናቂውን መስቀል
የጦርነት ጊዜዬም እስኪያልፍ
አልክድም አስጨናቂውን መስቀል
አንድ ቀንም በላይ ዘውዴ ነው።
፪፡ ያ አስጨናቂ መስቀል
የተናቀው ባለም
ፈጥሯል በኔ ታላቅ መገረም
ውዱ የአምላክ በግ
ለቀራንዮ መስቀል
ክብሩን ትቶ መጥቶልኛል።
ልምረጠው . . .።
፫፡ ባስጨናቂው መስቀል
በደሙም መታጠብ
ያሳየኛል ግሩም እምነት
በዚያ መስቀል ላይ ነው
ኢየሱስ የሞተው
ሊያፈስልኝ ለኔ ምሕረት።
ልምረጠው . . .።
፬፡ ላስጨናቂው መስቀል
ታማኝ እሆናለሁ
ኃፍረቱንም እችላለሁ።
አንድ ቀን ይጠራኛል
ወደ ራቀው ቤቴ
ክብሩን ለኔ ሊያወርሰኝ።
ልምረጠው . . .።

Exit mobile version