Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 564 ክርስቲያኖች ሆይ እንነሣ የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 564 ክርስቲያኖች ሆይ እንነሣ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ ክርስቲያኖች ሆይ እንነሣ
    እንገሥግስ በእልልታ
    የሱስ ነው ከኛ ጋራ።
    መስቀሉንም አንሸከም
    ለመከተል ብንደክም
    ሳይረዳን አይተወንም።
    በቅን መንገድ ይመራናል
    ከጉዳት ይጠብቀናል።
፪፡ የሱስ ገባ በጀግንነት
    ጦር ወደ ተፋፋመበት
    እንከተል በድፍረት።
    ለጌታ ሰንደቅ ዓላማ
    ተንቀን ብንታይ እንኳ
    ከእውነት አንዛባ።
    ይፈጸም የንጉሥ ተስፋ
    ክብሩም በኛ ይንሰራፋ።
፫፡ አርበኞች ሁነን በፍጥነት
    ብንዋጋ ለመሠረት
    ባለሙ ቅዱስ እውነት
    የሐሰት ምሽግ ይፈርሳል
    ክፋት ኃጢአት ድል ይሆናል
    የሱስ ብቻ ይነግሳል
    ምሕረቱ በሚታይበት
    ይሰፋል የወንጌል ትምህርት።
፬፡ ድንቅ ኃያል አምላክ ነው ስሙ
    የተሳለ ሰይፍ ነው ቃሉ
    ታጠቀ በእውነቱ
በሚገባ ድል ይነሳል
    ሁከት በሰላም ይተካል
   ሰው ከጥፋት ይድናል።
   የሚሠቃይ በባርነት
   በርሱ ያገኛል አርነት።
፭፡ አባቶች በእምነት ያዩት
   ጻድቃን የተነበዩለት
   ሰው ሆኖ ተወለደ
   ሕዝቡ እየቀለዱበት
    የሞተው በመስቀል እንጨት
   በግርማው ይገለጣል
   በመስቀሉ ላላፈሩ
   ያካፍላል ከክብረቱ።
፮፡ ለግዛቱ እንሰለፍ
    በሥራችን አንስነፍ
    ቀን በከንቱ አናሳልፍ
   ብርሃን በማይጠፋበት
   በሰማይ በሚሰጠን ቤት
   እናገኛለን ዕረፍት።
   ከዚች ምድር ስንሻገር
  ዕልል እያልን እንዘምር።

Exit mobile version