መዝሙር 561 የሱስን ብቻ ተስፋ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስን ብቻ ተስፋ
የሚያደርገው
በእርሱም የሚያምን
በእርግጥ ብፁእ ነው።
፪፡ ድካም ጉስቁልናም
ቢያስደነግጠው
በወንጌል የተሰጠው
መጽናናት ይብቃው።
፫፡ አንዳንድ ጊዜ የሱስ
በግልጥ ይታየናል
ሌላ ጊዜ ግን ፍጹም
ይሰወርብናል።
፬፡ ግን በሕሊናችን እንዲህ
ቢሰማንም
ከእርሱ የተሰጠን
ሰላም አይናወጥም።
፭፡ በየሱስ መሞት አምላክ
እንደ ታረቀን
መጽናናት ሊሆንልን
ወንጌሉ ነገረን።
፮፡ በደሙ መድኃኒትም
ተገኝቶልናል
ይህንም ላለም ሁሉ
መግለጥ ይገባናል።
፯፡ ዘወትር የቸር አምላክ ወዳጅ
ከመሆን
የሚበልጥ ብፅዕና
ወዴት ይገኝ ይሆን
፰፡ እስክናይህ ድረስ
በጭንቀት ስንኖር
ጌታ የሱስ ሰላምህ
በልባችን ይኑር።