መዝሙር 541 መሐሪ አምላክ ሆይ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መሐሪ አምላክ ሆይ ጸጋህን ስጠኝ፥
በርእሱ ከኃጢአትም አድነኝ፥
ወደ ዘላለም ሕይወት እንዲመራኝ
ጌታ ሆይ መንፈስ ቅዱስን ላክልኝ።
፪፡ የዓለም ብርሃን የንጋት ኮከብ ሁነህ፥
የሰውን ልጆች ወደ አንተ ለማቅረብ
ከወጣህ አንተን እመለከታለሁ፥
በምትመራኝ መንገድ እሄዳለሁ።
፫፡ በኃጢአት እንቅልፍ ለማንቀላፋት
እንድሞትም አልተውኸኝም ኦ አባት።
በጸጋህ ምሕረትን ስለ ሰጠኸኝ፥
ልቤን ገጸ በረከት ተቀበለኝ።
፬፡ ጌታ የሱስ ሆይ ለኔና ለሁሉ
የመቅሠፍትን ጽዋን ጠጣኸው በሙሉ።
እወድሃለሁ ባንተም አምናለሁ፥
በኃይልህም ከጥፋት እድናለሁ።