መዝሙር 53 በመስቀል የሱስ ሲሞትልን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በመስቀል የሱስ ሲሞትልን
ኃጢአታችንን አስወግዶአል።
ባለ – መታዘዝ የመጣውን፥
በፍቅሩ ከኛ አርቆልናል።
ቅዱሱ ኃጢአት የሌለበት፥
ስለኛ የሞትን ሥቃይ ቀምሶአል።
፪፡ ኃጢአት እንደ ቅርምዝ ቢጠቁር
እንደ በረዶ ያነጻልናል።
ጌታ በመስቀል ስለሞተ፥
ሕይወትና ጽድቅን አግኝተናል።
በእምነት ጌታን ስንማጠን፥
አበሳችንን ይሠርየዋል።
፫፡ በደላችንን ተሸክሞ
በግርፋቱ ቁስል ፈወሰን።
ጸጋና ምሕረቱን አብዝቶ፥
ከሞት ፍርሃት ጭንቀት አድኖናል።
በጥልቅ ፍቅሩ የተወጉትን፥
እጆቹና እግሮቹን ያሳየናል።
፬፡ በጎልጎታ የሞትህልን ሆይ
የድል ጌታ ክርስቶስ ተመስገን።
የማዳንን ጸጋ አብዝተህ፥
የዘላለም ሕይወትን ሰጠኸን።
በፍርድ ዕለት በፊትህ ስነቆም
ያባቴ ቡሩካን ግቡ በለን።