መዝሙር 525 ከአምላክ ፍርድ ልታድነኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከአምላክ ፍርድ ልታድነኝ
በመስቀል ሞት የገዛኸኝ፥
ኦ መድኅኔ ኦ አምላክ፥
መርገምን ከእኔ ደምስስ፥
ደምህን በኔ ላይ አፍስስ፥
እኔን ርጕሙን ባርክ።
ቅዱስ ደምህ ኃይል ይሁነኝ፥
ከኃጢአቴ ይጠበኝ።
ማሸነፍንም እንዳገኝ፥
የእምነትን ብርታት ይስጠኝ።
ጉዞዬንም ከጨረስሁ፥
እገባለሁ ወደ ዘላለም ብፅዕና።