መዝሙር 471 ድንቁን ታሪክ ንገረኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ድንቁን ታሪክ ንገረኝ ሰላዲስዋ ሀገር
ስለ የሱስ ፍቅርና ስለ የሱስ ክብር፥
እንዲገባኝ አድርገህ ታሪኩን ንገረኝ፥
ኃጢአት ያረከሰኝ ነኝ ፍቅሩም የማይገባኝ።
ድንቁን ታሪክ ንገረኝ፥(3)
ስለ ኢየሱሰ ፍቅር።
፪፡ በቀስታ ንገረኝ በጣም እንዲገባኝ
አስደናቂውን መዳን አምላክ የሰጠኝን፥
ብዙ ጊዜ ንገረኝ የማለዳ ጤዛ
ፈጥኖ እንደሚጠፋ እኔም እንዳይጠፋኝ።
ድንቁን ታሪክ . . .።
፫፡ አለስልሰህ ንገረኝ ድምጽህን አጣፍጠህ
ኢየሱስ እኔን ሊያድን እንደ መጣ አውቀህ።
ደጋግምና ንገረኝ የየሱስን ታሪክ
ደሙን ስላፈሰሰ ስሙን እንዳከብር።
ድንቁን ታሪክ . . .።