Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 468 የኢየሱስ ክቡር ፍቅር የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 468 የኢየሱስ ክቡር ፍቅር የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ የኢየሱስ ክቡር ፍቅር
ደስታ የሚሰጠን
ሸክማችንን ያቀላል
ቀናችንን ያበራል
ኀዘናችንን ያጠፋል
ፍርሃትን ያርቀዋል
ጨለማውን ያጠፋል
ብርሃኑን ያሳየናል።
፪፡ የኢየሱስ ክቡር ፍቅር
ዕንባችንን ያብሳል
ታላቅ ድፍረት ይሰጠናል
ፍርሃትን ለማሸነፍ
ሕይወታችንን ያድሳል
ስንሞት ይረዳናል
ወንዙን በሰላም አሻግሮ
በሰማይ ያኖረናል።
፫፡ ፍቅሩን እፈልገዋለሁ
ለማገልገል እንድችል፥
በአጠገቤ መሆኑን፥
እርሱ ይገልጽልኛል፣
ይባርከዋል ሥራዬን፥
መንገዴን ያቀናዋል፤
የጠፉትን ነፍስ ለማዳን፥
ከጥፋት ወደ ብርሃን።
፫፡ የኢየሱስ ፍቅር አለኝ
ለርሱ ይሁን ምስጋና፤
በዝማሬ ልወድሰው፥
ስለ ፍቅሩ ላብስር፤
እናመስግነው በኅብረት
ፍቅሩን በጣም እንረዳው
ኑ በኅብረት እንዘምር
አዲስ የሆነ መዝሙር።

Exit mobile version