መዝሙር 455 ወንድሜ ሆይ ቶሎ ና የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ወንድሜ ሆይ ቶሎ ና
ለምንስ ትዘገያለህ?
ጌታህም አንተን ይጠብቃል፥
ስፍራ ሊሰጥህ በርሱ ቤት።
ለምን? ለምን?
ለምን ቶሎ አትመጣም?
ለምን? ለምን?
ለምን ቶሎ አትመጣም?
፪፡ ወንድሜ ሆይ፥ ቶሎ ዳን
በጌታ በኢየሱስ ጸጋ።
ያለ እርሱ መድኃኒት የለህም፥
የማዳን መንገድ እርሱ ነው።
ለምን . . .?
፫፡ ወንድሜ ሆይ አትቆይ
የእርሱን ደኅንነት ተቀበል።
ወደ ጌታህ እይ በእምነት፥
በደልህን ይቅር ይላል።
ለምን . . .?
፬፡ ወንድሜ ሆይ፥ አትቆይ
የመከሩ ጊዜ ያልፋል።
ከመከራና ከድካም፥
እርሱ ጌታ ያድንሃል።
ለምን . . .?
