መዝሙር 453 የአምላካችን ተአምራት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የአምላካችን ተአምራት
በኃይሉ የሚያደርገው፤
ለመላ ዓለም የሚገለጥ፥
ይህ ለኛ ደስታችን ነው።
የከይሲን ኃይል ያሸንፋል፥
የወደቁትን ያነሣል።
፪፡ የአምላክ ቃል በታላቅ ግርማ
በዓለም ውስጥ ያሸንፋል፤
ኃጢአተኛው እጁን ሰጥቶ፥
ምሕረቱን ይለምናል።
በየሱስ ደም ይታጠባል፥
ለአምላክ ክብር ይሰጣል።
፫፡ ወደ ዘላለም ብፅዕና
የሚጓዙት ብዙ ናቸው፤
ከመላ ዓለም የሚመጡት፥
በክርስቶስ ተስፋ ያላቸው።
ገና አሉ የሚድኑ፤
በየሱስ ክርስቶስ የሚያምኑ።
፬፡ አሁን አዝመራው እንደነጣ
በዓይናችሁ ተመልከቱ፤
ኃጢአተኞቹን ለመጥራት፥
ተነሥታችሁ አገልግሉ።
ንቁ ቁሙ በአንድነት፥
አውጁ ያምላክን ስርየት።