መዝሙር 443 የዓለም ሀብት የኔ አይደለም የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የዓለም ሀብት የኔ አይደለም
ወርቁና ብሩም ይጠፋል፤
ግን የላቀ ሀብት በላይ አለኝ፥
የማይነገር ሀብት በሰው ቃል።
ኦ የፍቅር ጥልቀትና ሀብት፥
በየሱስ ያለው የፍቅር ሀብት።
ከወርቅና ከአልማዝ ይበልጣል፥
ብትታመንበት በየሱስ ኃይል።
፪፡ የዓለም ሀብት ኃላፊ ነው
ብልጽግናውም አይጠቅምም።
ግን ያለኝን የፍቅር ሀብቴን፥
ሞት እንኳን ሊነጥቀኝ አይችልም።
ኦ የፍቅር . . .።
፫፡ ከፍቅሩ ጋር ሲወዳደር
ዓለማዊ ሀብት ከንቱ ነው፥
እኔም ስለዚህ ሁሉን ትቼ፥
መጣሁ ወደ ጌታ ተጸጽቼ
ኦ የፍቅር . . .።
፬፡ ብልጽግናን መጥተህ ውሰድ
በነጻ ከየሱስ በትርፍ፤
ካስደናቂ ሕይወት ተካፈል፥
ከራብ ከጥማትም እንድታርፍ።
ኦ የፍቅር . . .።