Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 44 ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅመኝም የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 44 ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅመኝም የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅመኝም
የጠፋች ነፍሴን ሊያድናት አይችልም።
በመስቀል የፈሰሰው ደሙ አነጻኝ
የመድኅኔ ሞት ሕያው አደረገኝ።
ብርም ከቶ አያድነኝም
ወርቅ ቢሆን አይገዛኝም፥
ተገዛሁኝ በኢየሱስ ደም
በፍቅሩ ንጹህ ደም።
፪፡ ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅመኝም
የኃጢአት ሸክሜን አያነሣልኝም።
በመስቀል የፈሰሰው ደም አነሣልኝ
የመድኅኔ ሞት ዕዳዬን ከፈለው።
ብርም ከቶ . . .።
፫፡ ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅኝም
ትእዛዛትን ከመፈጸም አገደኝ።
በመስቀል የፈሰሰው ደም አስታረቀኝ፥
የመድኅኔ ደም ፍርሃነቴን አራቀው።
ብርም ከቶ . . .።
፬፡ ወርቅና ብርም ለመዳን አይጠቅመኝም
የሰማይንም ደጅ አይከፍትልኝም፥
በመስቀል የፈጸመው ደሙ አነፃኝ።
የመድኅኔ ሞት አዲስ ሕይወት ሰጠኝ።
ብርም ከቶ . . .።

Exit mobile version