መዝሙር 437 እንግዳ ነኝ እኔ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ እንግዳ ነኝ እኔ ስኖር በዚች ዓለም
ሀብቴም በሰማይ ነው ከዚህ ምንም የለኝ።
የሱስ ይጠራኛል ከሰማይ በር ከፍቶ፥
ከእንግዲህ ይህ ዓለም ፍጹም ቤቴ አይደለም።
ታማኝ ወዳጅ እንዳንተ እንደሌለኝ፥
ጌታ ሆይ፥ ታውቃለህ እኔን የሚያጽናናኝ።
የሱስ ይጠራኛል ከሰማይ በር ከፍቶ፥
ከእንግዲህ ይህ ዓለም ፍጹም ቤቴ አይደለም።
፪፡ ወደፊት ልራመድ ይጠባበቁኛል
የሱስ ይቅር ብሎኝ በሩን ከፍቶልኛል።
ምንም ድሀ ብሆን እኔን አይተወኝም፥
ከእንግዲህ ይህ ዓለም ፍጹም አይረባኝም።
ታማኝ ወዳጅ . . .።
፫፡ አፍቃሪ አዳኝ አለኝ በላይኛው አገር
ናፍቆቴን አልተውም ፊቱን እስካይ ድረስ።
በሰማይ ደጅ ቆሞ ይጠባበቀኛል፥
ከእንግዲህ ይህ ዓለም ፍጹም ቤቴ አይደለም።
ታማኝ ወዳጅ . . .።
