መዝሙር 423 በብፁዓን መኖሪያ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በብፁዓን መኖሪያ
ነዋሪ ርስት አለን፤
በየሱስ ደም ወደዚያ፥
ገብተን እንወርሳለን።
መስቀሉን ተሸክመን፥
መከራን ታግሠን፥
አክሊሉን እንድንጭን፥
እንጓዝ ወደ ሰማይ።
፪፡ ከሞትም ባሕር ወዲያ
ሞገዱ ጸጥ ይላል
ያሁኑ ችግር በዚያ፥
አልቆ ይለቀናል።
መስቀሉን . . .።
፫፡ የሱስ ያዘጋጀልን ቤት
ይከፈትልናል፤
ከምድር የተመረጡት፥
በዚያ ይቆዩናል።
መስቀሉን . . .።
፬፡ ከዓለማዊ ከንቱነት
ልባችን ወደ ላይ፤
ይናፍቃል ይመኛልም
የሱስን እስክናይ።
መስቀሉን . . .።