መዝሙር 422 ወዳንተ የሱስ ሆይ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ወዳንተ የሱስ ሆይ
ልቤ ይናፍቃል፤
የአምላክ በግ ሁነህ፤
ስለኔ ሙተሃል።
፪፡ ሰላም ለኔ ሰጠህ
ተሸክመህ ቅጣት፤
ታዳጊዬም ሆነህ፥
አወጣኸኝ ከሞት።
፫፡ ለኔም ባባቴ ቤት
ስፍራን አዘጋጀህ፤
ዓይናችን ያላየው፥
ብርሃኑም አንተ ነህ።
፬፡ ከዓለም መሄዴ
በደረሰ ጊዜ፤
ምራኝ በብርሃንህ፥
ልገባ አገሬ።
