መዝሙር 420 በዙፋኑ ፊት ድነው የቆሙቱ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በዙፋኑ ፊት ድነው የቆሙቱ
ነጭ ልብስም ለበሰው ለመድኃኒቱ።
ክብር የሚሰጡት፥
እኒያ ማን ናቸው።
እነዚያ ዳኑ በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም፥
ነጹም በበጉ ደም
እነዚያ ዳኑ በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም፥
ነጹም በበጉ ደም።
፪፡ እነዚያ ከታላቅ ጭንቀት መጥተው
በበጉ ደም ልብሳቸውን አጥበው፤
የሱስን ተቀብለው፥
የዳኑቱ ናቸው።
እነዚያ ዳኑ . . .።
፫፡ ለዘላለም ድነው ከዚህ ምድር ጻር
በበገና በመሰንቆም አውታር፥
በማይሻር አዲስ ደስታ፥
መዝሙር ያሰማሉ።
እነዚያ ዳኑ . . .።