መዝሙር 413 በኑሮ ውቅያኖስ ውስጥ ማዕበል ሲነሣ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በኑሮ ውቅያኖስ ውስጥ ማዕበል ሲነሣ
መከራ ሲያስጨንቀኝ ሞገድ ሲያውከኝ፤
ተስፋዬን በክርስቶስ ላይ አደርገዋለሁኝ፥
በምሕረቱ ዕረፍትን ይሰጠኛል።
በየሱስ ማዕበሉን እቋቋማለሁ፥
በየሱስ ሞገድንም ቢሆን አልፈራም።
በደኅንነት ኃይሉ ጌታ ይጠብቀኛል፥
የጥንት አምባ የሱስን አምነዋለሁ።
፪፡ ነፍሴን ከክፉ ጠብቆ ሰላም ይሰጠኛል
የሚያውከኝን ጸጥ ያደርጋል በቃሉ።
መሪዬና አዳኜ በርሱ እታመናለሁ፥
ረድኤት ሲያስፈልገኝ ከኔ ጋር ነው።
በየሱስ ማዕበሉን . . .።
፫፡ ወዳጄ መድኃኒቴ መሠረቴ እርሱ ነው
ኀዘኔን አርቆልኝ ጽናቱን ሰጥቶኛል።
የሱስ ያዘጋጀልኝን የዕረፍት ቦታ፥
በእምነት ባሻገር አየዋለሁኝ።
በየሱስ ማዕበሉን . . .።