መዝሙር 411 በእምነት አያለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በእምነት አያለሁ
የቀራንዮን በግ መድኃኒቴን።
ጸሎቴን አድምጠው፥
ኃጢአቴን ደምስሰው፥
ሕይወቴን በሙሉ ተረከበው።
፪፡ ጸጋህን አፍስስልኝ
ልቤንም አጽናልኝ አነቃቃኝ።
ስለኔ የሞትኸው፥
ፍቅርህ በልቤ ውስጥ፥
ለዘላለም ይሁን ሕያው እሳት።
፫፡ ቀን ሲጨልምብኝ
ኀዘን ሲጸናብኝ መሪዬ ሁን።
ጨለማውን አብራ፥
ዕንባዬን አብሰው፥
እንዳልተውህ እርዳኝ መድኃኒቴ።
፬፡ የሕይወቴን ተስፋ
ሞት ሲጨልምብኝ በላዬ ላይ፤
አዳኜ ቅረበኝ፥
በፍቅር ክበበኝ፥
የዋጀሃትን ነፍስ ተቀበለኝ።