መዝሙር 408 ክርስቲያን በመሆኔ እደሰታለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክርስቲያን በመሆኔ እደሰታለሁ
በጌታ በየሱስ ስም አምኛለሁ።
ኃጢአቴ በሙሉ ተፍቆልኛል፥
በሰማይ አዲስ ቤት ይጠብቀኛል።
፪፡ ክርስቲያን በመሆኔ እደሰታለሁ
በጌታ በየሱስ ስም አምኛለሁ።
መጽሐፍ ቅዱሴንም አነበዋለሁ፥
በቅዱሱ ቃሉም እባረካለሁ።
