መዝሙር 400 ደስ ይበለኝ ኀዘን ይራቅልኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ደስ ይበለኝ ኀዘን ይራቅልኝ
እግዚአብሔር ይወደኛል።
አምላካችን አባት ከሆነልኝ፥
ስለ ልጁ እርሱ ያስባል።
በየደቂቃው የሚደርሰኝን፥
አባቴ በፍቅሩ ልኮታል።
ለየቀኑም የሚጠቅመኝን
ደስታም ኀዘንም ያካፍላል።
፪፡ ጩኸቴን ለመስማት አይሰለችም
ሸክሜንም ያነሣልኛል።
በድካሜ ከኔ ዘንድ አይለይም፥
ስሙም መካር ኃያል ይባላል።
ክቡር ገንዘቡ እንዳይጠፋበት፥
እርሱ ራሱ ይጠነቀቃል፤
እንደ ቀኑም ኃይሉ ሊሆንለት፥
ልጁን ጸጋው ያበረታዋል።
፫፡ አምላኬ እንዲህ ስታስብልኝ
እኔም ሐሳቤን ልተው እርዳኝ።
እምነትን ከቃልህ ጨምርልኝ፥
በዚህም ወዳገሬ ምራኝ።
ደስ ሲለኝ ስጨነቅም በኀዘን፥
አንተ ሁሉን እንደ ሰጠኸኝ፤
ተስፋህን ተቀብዬ ለማመን፣
ጌታ ሆይ፥ አንተ አስተምረኝ።
