መዝሙር 393 ነፍሴ ወዳምላክሽ ተጠጊ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ነፍሴ ወዳምላክሽ ተጠጊ
እርሱንም ተስፋሽ አድርጊ።
በመከራ ስትበሳጪ
ረድኤት ከእርሱ ለምኚ።
በአምላኩ የሚታመን
ባሸዋ አይሠራም ቤቱን።
፪፡ የሰላም ጊዜን ጌታ ያውቃል
የሚጠቅምሽን ያስባል።
ጸሎትሽን እርሱ ይሰማል
የለመንሽውን ይሰጣል።
ባልታሰበ ጊዜ ደግሞ
ረድኤትሽ ይመጣል ፈጥኖ።
፫፡ ችግርሽ እንኳ ቢበረታ
አምላክ የረሳሽ አይምሰልሽ።
በኀዘን ፈንታ ደስታ ሰጥቶሽ
ያስወግዳል ትካዜሽን።
ሁልጊዜ ይወድሻል
መዳንሽንም ያስባል።
፬፡ ታላላቆቹን ዝቅ ለማድረግ
ለአምላካችን ቀላል ነው።
ምስኪኖችንም ለማበልጠግ
ለእርሱ የማያስቸግር ነው።
ልዑል አምላክ በግብሩ
ያስገርማል ድንቅ ምክሩ።