መዝሙር 392 ጽናት በየሱስ እጆች የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ጽናት በየሱስ እጆች
ዕረፍትም በክንዱ
ደስታም በፍቅሩ ጥላ
ባገኝ ይበቃኛል።
በሰማያዊ አገር
ቅዱሳን መላእክት ሁሉ
ላምላክ ይዘምራሉ
በደስታ ሁሉ ቀን።
ጽናት በየሱስ እጆች
ዕረፍትም በክንዱ
ደስታም በፍቅሩ ጥላ
ባገኝ ይበቃኛል።
፪፡ ጽናት በየሱስ እጆች
ረድኤት በኀዘንም
ዓለም እኔን ሲፈትን
ኃጢአት አይገዛኝም።
ጥርጣሬ ሆነ ኀዘን
የሚያስፈራ ሁሉ
ለጥቂት ጊዜ ብቻ
እኔን ያሠቃያል።
ጽናት በየሱስ እጆች
ረድኤት በኀዘንም
ዓለም እኔን ሲፈትን
ኃጢአት አይገዛኝም።
፫፡ የሱስ የኔ አዳኝ ነው
ስለኔ ሞቶአል።
የሱስ ነው የኔ አምባ
በእርሱ እጽናናለሁ።
ስለዚህም ልታገሥ
ጨለማው እስኪያልፍ ድረስ
ወዲያ እስክደርስም
ቀን ወደ አለበት።
የሱስ የኔ አዳኝ ነው
ስለኔ ሞቶአል
የሱስ ነው የኔ አምባ
በእርሱ እጽናናለሁ።