መዝሙር 390 ነፍሶች ሁሉ በኃጢአት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ነፍሶች ሁሉ በኃጢአት
የተጨቆናችሁ፥
በውነት ጌታችን ፈዋሽ ነው
በቃሉ ብታምኑ።
በርሱ ጽኑ፥ በርሱ ጽኑ፥
በጌታ ጽኑ።
ይቅር ባይ ነው፥ ይቅር ባይ ነው፥
መድኃኒታችን።
፪፡ የሱስ ለኛ ሲል በመስቀል
ደሙን አፈሰሰ፥
ከባድ ከሆነውም ኃጢአት፥
እርሱ ያነጻናል።
በርሱ ጽኑ . . .።
፫፡ አዎን፥ የሱስ መሪያችን ነው
ለዕረፍት የሚጠራን፥
በርሱ ብናምን ሳንዘገይ
ደስታ ይሰጠናል።
በርሱ ጽኑ . . .።
፬፡ ወደርሱ እንሂድ ባንድነት
ወደ ክቡር ጌታ፥
በዚያችም ሀገር በደስታ
ከርሱ ጋር እንድንኖር።
በርሱ ጽኑ . . .።