መዝሙር 349 ጌታ የሱስ ክርስቶስ ራራልን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ጌታ የሱስ ክርስቶስ ራራልን፤
በምሕረቱ ይጠራናል።
ቸሩ ወዳጅ ይፈልገናል፥
መድኃኒትም ይሆነናል።
ቃሉን አሁን ስናዳምጠው፥
ልባችንን አናደንዝዘው።
፪፡ ዛሬ ይጠራናል በፍቅር፤
እሙን መድኃኒታችን ነው።
አንድ ቀን ግን ሲመጣ በክብር፥
ጻድቅ ፈራጅም እርሱ ነው።
ዛሬ እርሱን ብንቀበል፥
ከፍርድ ነጻ እንሆናለን።
