መዝሙር 277 እንደ ፈቃድህ ይሁን ጌታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ እንደ ፈቃድህ ይሁን ጌታ
አንተ ሠሪዬ ነህ እኔም ሸክላ።
እንደ ፈቃድህ አስተካክለኝ፥
እንደ ፈቃድህ ልሁን ጌታ።
፪፡ እንደ ፈቃድህ ይሁን ጌታ
መርምር ሕይወቴን በኔ ፈንታ፥
እንደ በረዶ አንጻኝ ልጥራ፥
በፊትህ ልስገድ በትሕትና።
፫፡ እንደ ፈቃድህ ይሁን ጌታ
ጎስቋላ ነኘ ጸሎቴን ስማ፥
ግርማና ክብር የአንተ ነው፥
ዳስሰህ ፈውሰኝ ቅዱስ ጌታ።
፬፡ እንደ ፈቃድህ ይሁን ጌታ
በቅዱስ መንፈስ ተሞልቼ፥
ሁለመናዬ ተለውጦ፥
አንተን ላገልግል በሕይወቴ።
